ሪፖርት| ደሴ ከተማ ከመመራት ተነስቶ ጣፋጭ ሶስት ነጥብ አሳክቷል !

5 ግቦች በተቆጠረቡት በረፋድ ሶስት ሰዓት ጨዋታ ደሴ ከተማ ባለቀ ደቂቃ ግብ አስቆጥሮ አሸንፏል። አምስቱም ግቦች በሁለተኛው አጋማሽ በተቆጠሩበት በዚህ ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ ሁለቱም ቡድኖች ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ወደሜዳ በመግባታቸው ኳስን ወደፊት ገፍተው ከመጫወት ይልቅ ወደኋላ አፈግፍገው በመከላከል ሲጫወቱ ተስተውለዋል።

በሁለተኛው አጋማሽ ሁለቱም ቡድኖች የተጫዋቾች ቅያሪ በማድረግ ተሽሎ ለመገኘት ጥረት አድርገዋል። ቀድመው ቅያሪ ያደረጉት ደሴ ከተማዎች ከደብረብርሃን ከተማ የጨዋታ ብልጫ ቢወስዱም በ54ኛው ደቂቃ የደሴ ተጫዋቾች ኳስን እየገፉ ወደፊት ሄደው ሳይመልሱ ሲቀሩ ደብረብርሃኖች ያገኙትን እድል በሄኖክ አየለ አማካኝነት ወደግብነት ቀይረው መሪ መሆን ችለዋል። ነገር ግን በመሪነት የቆዩት ለአራት ደቂቃ ብቻ ነበር። በኳስ ቁጥጥር ተሽለው የተገኙት ደሴ ከተማዎች በጨዋታው ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ በታየው በበሱፍቃድ ነጋሽ አማካኝነት የአቻነት ግብ አስቆጥረዋል።
የአቻነት ግብ ከተቆጠረ በኋላ ሁለቱም ቡድኖች በጥንቃቄ ሲጫወቱ የተስተዋሉ ሲሆን ለ20 ደቂቃዎች ያህል አስቆጪ የሚባል የግብ ሙከራ አላስመለከቱም። ተቀይሮ የገቡት አቡሸ ደርቤ እና  ሚካኤል ለማ በእርስ በእርስ ቅብብሎሽ ወደተቃራኒ ቡድን በሚሄዱበት ግዜ በአቡሽ ደርቤ ላይ የደብረብርሃን ተከላካዮች ጥፋት ሰርተውበት ቅጣት ምት ተሰቷቸዋል። በ82ኛው ደቂቃ የቆመ ኳስ ተፈሠ ሠርካ ወድግብ ክልል አሻምቶ ዘሪሁን ዐቢይ ኳስና መረብ አገናኝቶ ደሴ ከተማ መሪ መሆን ችለዋል።

ደሴ ከተማ 2ለ1 እየመራ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ግዜ አልቆ ተጨማሪ በታየው 6 ደቂቃ ውስጥ ሁለት ግቦች የተቆጠሩ ሲሆን በ90+3 ደቂቃ ላይ ኢዮብ አስራት የደሴ ከተማ ተከላካዮች የሰሩትን ሰህተት በመጠቀም ደብረብርሃን ከተማን አቻ አድርጓል።
ተጨማሪ ደቂቃ ሊያልቅ ሽርፍራፊ ሰከንዶች ቀርተው እያለ በድጋሚ ደብረብርሃን ከተማዎች ጥፋት ሰርተው የቆመ ኳስ ለደሴ ከተማ ተስጥቷቸዋል።ያገኙትን ቅጣት  ምት ኳስ ከመስመር አከባቢ ታፈሰ ሰርካ አሻምቶ ዘሪሁን ዐቢይ ጭፎ ወዴግብነት ቀይሮ ጨዋታው 3ለ2 በሆነ ውጤት በደሴ ከተማ አሸናፊነት ተጠናቋል።

©Soccer Ethiopia

ደብረብርሃን ከተማ ከደሴ ከተማ ቁጥራዊ መረጃዎች

ደብረብርሃን ከተማ     ደሴ ከተማ
የተጫወተው -8          የተጫወተው -8
አሸነፈ-2                        አሸነፈ-4
አቻ-1                            አቻ-3
ተሸነፈ-5                        ተሸነፈ -1
ያስቆጠረው -8             ያስቆጠረው -11
የተቆጠረበት -14            የተቆጠረበት -6
ነጥብ-7                       ነጥብ -15
ደረጃ -12                       ደረጃ-4
የእርስ በርስ ግንኙነቶች
👉3 ጊዜ ተገናኝተው ደብረብርሃን ከተማ 1 ጊዜ ሲያሸንፍ ደሴ ከተማ  ደግሞ 2 ጊዜ አሸንፏል።
👉ደብረብርሃን ከተማ አንድ ጎል ሲያስቆጥር ደሴ ከተማ ደግሞ ስድስት ጎሎችን አስቆጥሯል ።
👉2012(ደሴ ከተማ 4-0 ደብረብርሃን ከተማ)
👉2013(ደብረብርሃን ከተማ 0-2 ደሴ ከተማ፣ ደሴ ከተማ 0-1 ደብረብርሃን ከተማ)

http://t.me/dessiecityfootballclub

የወሎ ደርቢ ቁጥራዊ መረጃዎች

ደሴ ከተማ ከወሎ ኮምቦልቻ   ቁጥራዊ መረጃዎች‼️

ደሴ ከተማ    ወሎ  ኮምቦልቻ
የተጫወተው -7          የተጫወተው -7
አሸነፈ-3                        አሸነፈ-1
አቻ-3                               አቻ-2
ተሸነፈ-1                           ተሸነፈ -4
ያስቆጠረው -9             ያስቆጠረው -5
የተቆጠረበት -5            የተቆጠረበት -11
ነጥብ-12                        ነጥብ -5
ደረጃ -4                          ደረጃ-13

የእርስ በርስ ግንኙነቶች
👉8 ጊዜ ተገናኝተው ደሴ ከተማ 3 ጊዜ ሲያሸንፍ ወሎ ኮምቦልቻ ደግሞ አንድ ጊዜ ያሸነፈ ሲሆን በ4ቱ ደግሞ አቻ ተለያይተዋል ።
👉ደሴ ከተማ 5 ወሎ ኮምቦልቻ ደግም 2 ጎሎችን አስቆጥረዋል።
👉2010 ( ወሎ ኮምቦልቻ 2-0 ደሴ ከተማ,ደሴ ከተማ 2-0 ወሎ ኮምቦልቻ )
👉2011(ወሎ ኮምቦልቻ 0-0 ደሴ ከተማ,ደሴ ከተማ 0-0 ወሎ ኮምቦልቻ )
👉2012 (ወሎ ኮምቦልቻ 0-0 ደሴ ከተማ( 1 የወዳጅነት አንድ ደግሞ የከፍተኛ ሊግ ጨዋታ )
👉2013( ወሎ ኮምቦልቻ 0-2 ደሴ ከተማ, ደሴ ከተማ 1-0 ወሎ ኮምቦልቻ )

http://t.me/dessiecityfootballclub

ሪፖርት| የጦሳ ፈርጦቹን ከጦና ንቦቹ ያገናኘው የኢትዮጵያ ዋንጫ ሁለተኛ ዙር ጨዋታ በጦና ንቦቹ አሸናፊነት ተጠናቋል !!

ሀዋሳ ላይ የፕሪምየር ሊጉን ክለብ ወላይታ ድቻን ከደሴ ከተማ ጋር ያገናኘው መርሀግብር ጥሩ የሆነ ፉክክርን አስመልክቶን በወላይታ ድቻ ድል አድራጊነት ተፈፅሟል። ተመጣጣኝ የሚመመስል የጨዋታ ቅርፅን ነገር ግን የወላይታ ድቻ የተደራጀ የማጥቃት ቅርፅን በተመለከትንበት ጨዋታ በቀዳሚው የጨዋታ አጋማሽ ድቻዎች መሐል ሜዳውን በአግባቡ ተቆጣጥሮ በመጫወት እና በተለይ ደግሞ የደሴ ተከላካዮች የሚሰሩትን የቅብብል ስህተት በመጠቀም ግቦች ለማስቆጠር በድግግሞሽ ጫና ሲፈጥር ተመልክተናል። 21ኛው ደቂቃ ላይ የደሴ ተጫዋቾች ኳስን ሲቀባበሉ የፈጠሩትን ስህተት ቢኒያም ፍቅሬ በፍጥነት ነጥቆ ከፀጋዬ ብርሀኑ ጋር አንድ ሁለት ቅብብልን ካደረገ በኋላ ፀጋዬ በመጨረሻም ወደ ውስጥ ያሳለፈውን ኳስ ተጠቅሞ ቢኒያም ከመረብ አሳርፎ የጦና ንቦቹን መሪ አድርጓል። ደሴዎች ኳስን በመቀባበል ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመግባቱ ረገድ ቢሳካላቸውም በአንድ ሁለት ቅብብል ወቅት በሚፈጥሩት ስህተት መጋለጣቸው ያልቀረለት ቡድኑ ተጨማሪ ግብን ለማስተናገድ ተገደዋል። ጨዋታው ሊገባደድ 45+1 ላይ አብነት ደምሴ ለቢኒያም የሰጠውን ኳስ ፀጋዬ ብርሀኑ በግራ የግብ ክልል ገፋ ካደረገ በኋላ ሁለተኛ ጎል በማድረግ ወደ መልበሻ ክፍል በ2ለ0 ውጤት አምርቷል።


ከዕረፍት የተመለሰው የሁለቱ ቡድኖች መርሀግብር ቀጥሎ በንፅፅር የወላይታ ድቻ የበላይት የታየበት ነበር። መሐል ሜዳውን አሁንም ተቆጣጥረው ወደ መስመር በመለጠጥ ሲጫወት የነበረው ቡድኑ ከፍ ባለ ተገሳሽነት ሦስተኛውን ግብ አግኝተዋል። 58ኛው ደቂቃ ላይ ከራስ ሜዳ ኳስን ለማስጀመር ሲሉ ስህተቶቻቸው በጉልህ የሚታይባቸው ደሴዎች በተጠቀሰው ደቂቃ አብነት ደምሴ ነጥቆ ከብዙአየው ጋር ካደረገው ቅብብል በኋላ አበባየው አጂሶ ወደ ግራ የጣለውን ኳስ ፀጋዬ በቶሎ ነፃ ቦታ ለነበረው ዮናታን ኤልያስ አቀብሎት አማካዩ ሦስተኛዋን ጎል በማስቆጠር ጨዋታው ወደ 3ለ0 ተሸጋግሯል። ሦስት ጎልን ካስተናገዱ በኋላ ወደ ጨዋታ ቅኝት ውስጥ በይበልጥ የገቡት ደሴ ከተማዎች ከሽንፈት ያላዳናቸውን ኳስ 63ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥርዋል። በረጅሙ ከግራ በኩል የደረሰውን ኳስ በድቻ ተከላካዮች መሐል ሾልኮ በመውጣት ተቀይሮ የገባው ካሳሁን አስቆጥሮ ጨዋታው በወላይታ ድቻ የ3ለ1 ድል አድራጊነት ተቋጭቷል።

ምንጭ: ሶከር ኢትዮጵያ

ሪፖርት| ደሴ ከተማ ፣ስልጤ ወራቤ እና ሀምበሪቾ ተከታታይ ድል ሲያስመዘግቡ ኮልፌ ቀራንዮ ተሸንፏል


✅ሆሳዕና ላይ የአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች እሁድ እና ሰኞ የተካሄዱ ሲሆን የመጀመሪያ የነበረው የዳሞት ከተማ አና የሮቤ ከተማ ጨዋታ በሮቤ ከተማ 2-1 አሸናፊነት ተጠናቋል። ሮቤ ከተማ ከተከታታይ 3 ጨዋታ ሽንፈት በኋላ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል።

✅ሁለት ግብ የተመለከትንበት የመጀመሪያ አጋማሽ ጨዋታ በእንቅስቃሴ ረገድ ፈጣን የሆነና በግብ ሙከራ የታጀበ ሲሆን በጨዋታው የመጀመሪያ 10 ደቂቃ የዳሞት ከተማ የበላይነት የታየበትና ለግብ የቀረቡ ሙከራዎች እና የግቡ አግዳሚ የመለሰባቸው አጋጣሚ ይጠቀሳል። በ5ኛው ደቂቃ ሮቤ ከተማዎች ያገኙትን ኳስ በመልሶ ማጥቃት  በአማን ወርቁ አማካኝነት የመጀመሪያ ግባቸውን አስቆጥረዋል። ከግቧ መቆጠር በኋላ ሮቤ ከተማዎች ሁለተኛ ግብ ለማስቆጠር ተጭነው በመጫወት እና ዳሞት ከተማዎች በበኩላቸው የሮቤ ከተማዎችን ጫና ለመቋቋም በማፈግፈግ የተጫወቱ ሲሆን በ13ኛው ደቂቃ ሮቤ ከተማዎች በጥሩ ቅብብል ያገኙትን ኳስ በድጋሚ በፊት መስመር ተጫዋቻቸው አማን ወርቁ በጨዋታው ለራሱ እና ለቡድኑ ሁለት ግብ በማስቆጠር ሮቤ ከተማ 2-0 እዲመራ ማድረግ ችሏል። በዚህ እንቅስቃሴ ሌላ ተጨማሪ ግብ ሳይቆጠር  ወደ መልበሻ ክፍል መግባት ችለዋል።

✅በሁለተኛው አጋማሽ ተነቃቅተው የገቡት ዳሞት ከተማዎች ውጤቱን ለመቀልበስ ተጭነው የተጫወቱ ሲሆን ባንፃሩ ሮቤ ከተማዎች በመጀመሪያ አጋማሽ ያስመዘገቡትን ውጤት ለማስጠበቅ ወደ ኋላ በማፈግፈግ ተጫውተዋል። ዳሞት ከተማዎች ከሽንፈት ያላዳነቻቸውን ግብ በ83ኛው ደቂቃ ላይ የተገኘውን ፍፁም ቅጣት ምን ሳምሶን ቁልጭ በማስቆጠር ጨዋታው በሮቤ አሸናፊነት ሊጠናቀቅ ችሏል።

✅የስልጤ ወራቤ እና የኮልፌ ክ/ከተማን ጨዋታ በርከት ባለ ደጋፊ ሲደገፍ የነበረው ስልጤ ወራቤ በጠባብ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። የመጀመሪያው አጋማሽ በጣም ውጥረት የተሞላበት እና ኃይል የተቀላቀለበት ጨዋታ እና ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ የነበረበት ሲሆን በግብ ሙከራ ረገድ ስልጤ ወራቤ የተሻለ ሲሆን በ30ኛው ደቂቃ ሳዲቅ ሴቾ በማስቆጠር ስልጢ ወራቤ 1-0 በሆነ ውጤት እየመራ ወደ መልበሻ ክፍል እንዲገቡ ማድረግ ችሏል።

✅ሁለተኛው አጋማሽ ላይም ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ የታየበት ጨዋታ እና ደቂቃዎች በገፉ ቁጥር ኮልፌ ክ/ከተማ ግብ ለማስቆጠር ፣ በስልጤ ወራቤ በኩል ደግሞ ውጤትን ለማስጠበቅ የተቻላቸውን ሲያደርጉ ተመልክተናል። በጨዋታው መጠናቀቂያ ሰዓት አከባቢ በስልጤ ወራቤ በኩል የሰዓት ማባከን ሲስተዋል ነበር። ጨዋታው በዚህ ሁኔታ ምንም ተጨማሪ ግብ ሳይቆጠር ስልጤ ወራቤን ጣፋጭ ድል አስገኝቷል። በአንፃሩ ኮልፌ ክ/ከተማ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ የመጀመሪያ ሽንፈቱን ቀምሷል።

✅ደሴ ከተማ እና ሶዶ ከተማን  ባገናኘው ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ የደሴ ከተማዎች የበላይነት የታየበትና በኳስ ቁጥጥሩም ተሽለው የታዩበት አጋማሽ ነበር ። ሶዶ ከተማዎች ጨዋታውን በማፈግፈግ እና ረጅም ኳስ በመጠቀም ወደ ግብ ለመድረስ ሲሞክሩ ታይተዋል። በ31ኛው ደቂቃ ላይ በሶዶው ግብ ጠባቂ ስህተት የተገኘችውን ኳስ በአከር ቻም አማካኝነት በማስቆጠር ደሴ ከተማን መሪ አድርጎ ወደ መልበሻ ክፍል መግባት ችለዋል።


✅በሁለተኛው አጋማሽም ምንም ግብ ያላየንበት አጋማሽ ሲሆን በጨዋታውም ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ ቢታይም ሶዶ ከተማዎች ከሽንፈት ሊያድናቸውን የሚችለውን ግብ ለማስቆጠር ቢጥሩም ማስቆጠር ተስኗቸው ሽንፈት ማስተናገድ ችለዋል። ደሴ ከተማዎችም ከእረፍት በፊት ባስቆጠሩት ብቸኛ ግብ ጣፋጭ ድል አስመዝግበው ምድባቸውን መምራት ጀምረዋል ።

✅ ሀምበርቾ ዱራሜ እና ኦሜድላን ያገናኘው ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ ሀምበርቾ ዱራሜ በሙሉ የበላይነት የተጫወቱ ሲሆን በአንፃሩ ኦሜድላዎች የተጋጣሚን ጨዋታ ለማበላሸት እና ረጃጅም ኳሶችን ለመጠቀም በማሰብ ተጫውተዋል። ሆኖም በ29ኛው ደቂቃ ቃልአብ በጋሻው የመታውን ኳስ በመጭረፍ ዳግም በቀለ ሀምበርቾ ዱራሜን መሪ ማድረግ ችሏል።
✅ሁለተኛው አጋማሽ እንደተጀመረ በ49ኛው ደቂቃ ከመስመር የተሻገረውን ኳስ ዳግም በቀለ በግንባር በማስቆጠር አንበሪቾ ዱራሜን 2-0 እንዲመራ ማድረግ ችሏል። ጨዋታው በዚሁ እየቀጠለ ባለበት ሁኔታ በ73ኛው ደቂቃ ታምራት አዲሱ ግሩም የሚባል ግብ በመቀስ ምት በማስቆጠር  ለኦሜድላ የመጀመሪያውን ግብ የሆነና ውጤቱንም ወደ 2-1 ማጥበብ የቻለበት ነበር። ጨዋታውም ተጨማሪ ግብ ሳይቆጠርበት በአንበሪቾ ዱራሜ አሸናፊነት ተጠናቋል።

✅ጨዋታው ሰኞ እለት ሲቀጥል ነገሌ አርሲዎች አሰልጣኛቸውን ከቅጣት መልስ ያገኙበት የመጀመሪያ ጨዋታ እና ጅማ አባጅ ፋሮች ደግሞ አሰልጣኛቸውን ካሰናበቱ በኋላ ያደረጉት የመጀመሪያ ጨዋታ ነበር። ጥሩ እንቅስቃሴ የታየበት ጨዋታ የነበረ ሲሆን በአርሲ ነገሌዎች የጨዋታ ብልጫ እና በጅማ አባ ጅፋር መልሶ ማጥቃት የታየበት እና በሁለቱም በኩል ጥሩ የሆነ የግብ ሙከራ የታጀበ የመጀመሪያ አጋማሽ ተመልክተናል። በ20ኛው ደቂቃ ከመዕዘን የተሻገረውን ኳስ ሱራፌል ፍቃዱ በማስቆጠር ጅማ አባ ጅፋርን መሪ ማድረግ ችሏል።

✅በሁለተኛው አጋማሽ እንደ መጀመሪያው አጋማሽ ነገሌ አርሲ ተደጋጋሚ የግብ ሙከራ ያደረጉ ቢሆንም በጅማ አባ ጅፋሩ ግብ ጠባቂ ዮሐንስ በዛብህ አማካኝነት ማስቆጠር አልቻሉም። በ47ኛው ደቂቃ  የጅማ አባጅፋሩ አጥቂ ዳዊት ፍቃዱ ግብ በማስቆጠር መሪነታቸውን ማጠናከር ችሏል። በነጌሌ በኩል ሰለሞን ገመቹ ከፊት መስመር ጥሩ እንቅስቃሴ ካደረጉት ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው። በጅማ አባ ጅፋር በኩል ጥሩ የማጥቃት እንቅስቃሴ ሲያደርግ የታየው አሚር አብዲ በ61ኛው ደቂቃ ተጨማሪ ግብ በማስቆጠር የጅማ አባ ጅፋሮችን አሸናፊነት ማረጋገጥ ችሏል። ጅማ አባጅፋር በምክትል አሰልጣኛቸው በመመራት ርቋቸው የቆየውን ሦስት ነጥብ አሳክተዋል።

✅ የዕለቱ የመጨረሻ የነበረው የገላን ከተማ እና የቡራዩ ከተማ ጨዋታ ሲሆን በጨዋታውም ቡራዩ ከተማ 1-0 በሆነ ጠባብ ውጤት በማሸነፍ ተከታታይ ድል ማስመዝገብ ችሏል። በመጀመሪያ አጋማሽ  ጥሩ ትንቅንቅ እና አልሸነፍ ባይነት የታየበት ሲሆን ጨዋታው በጀመረ በ20 ደቂቃ የቡራዩ ከተማው የፊት መስመር ተጫዋች እንዳለማው ደሳለኝ ግሩም በሆነ አጨራረስ  ቡራዩ ከተማን አሸናፊ ያደረገች ግብ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን ጨዋታው በእንደዚህ ዓይነት መልኩ የመጀመሪያ አጋማሽ ተጠናቆ ወደ መልበሻ ክፍል መግባት ችለዋል።

✅በሁለተኛው አጋማሽም በተመሳሳይ ውጥረት የበዛበት ጨዋታ ሲስተዋል ገላን ከተማ ከሽንፈት ለመዳን ጫና በማሳደር ግብ ለማግባት ሲሞክሩ ተስተውሏል። በአንፃሩ ቡራዩ ከተማ በመጀመሪያው አጋማሽ ያገኘውን የግብ ብልጫ ለማስጠበቅ ወደ ኋላ አፈግፍጎ ሲጫወት ተስተውሏል። ሆኖም የገላን ከተማዎች ጥረት ሳይሳካ ቀርቶ ሽንፈት ማስተናገድ ተገደዋል። ቡራዩም ጣፋጭ ሦስት ነጥቡን በተከታታይ ማሳካት ችሏል።

ምንጭ:ሶከር ኢትዮጵያ

ቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ|ደሴ ከተማ ከፌዴራል ፖሊስ

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ የመጀመሪያ ዙር የመጨረሻ (9ኛ ሳምንት) ጨዋታዎች ነገ መካሄድ የሚጀምሩ ሲሆን የመክፈቻ ጨዋታ የሆነውን ደሴ ከተማ ከፌደራል ፖሊስ የሚያደርጉትን ጨዋታ በቅድመ ጨዋታ ዳሰሳ አምዳችን ተመልክተነዋል ።

ወደ ላይኛው የኢትዮጵያ ሊግ ወደሆነው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ለማደግ አንደኛ ሆኖ ማጠናቀቅ መስፈርት በሆነበት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በዚህ ሳምንት ፍፃሜውን የሚያገኝ ሲሆን በርካታ ፉክክር እየታየበት ይገኛል። በዚህ ምድብ ከሚገኙ ክለቦች አንዱ የሆነው ደሴ ከተማ ነገ የመጨረሻውን ጨዋታ የሚያከናውን ሲሆን ከአጀማመሩ አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ ቢችልም ባለፉት ተከታታይ ሳምንታት ነጥብ ነጥብ መጣሉ እና ሽንፈት ማስተናገዱ የመሪነት ቦታውን ቢያስረክብም ከመሪው ያለውን የ2 ነጥብ ልዩነት ለማጥበብ ወደሜዳ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል ። ባለፉት የውድድር ዘመናት በመጀመሪያው ዙር የነበረበትን ክፍተት አሻሽሎ የጀመረው ደሴ ከተማ ጥሩ ነጥቦችን መሰብሰብ ቢችልም በርካታ ተጫዋቾች ጉዳት ማስተናገዳቸው ባለፉት አራት ጨዋታዎች ማግኘት ከነበረበት 12 ነጥብ 4 ነጥብ ብቻ እንዲሰበስብ አድርጎታል። በተለይ ደግሞ ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች በኤሌክትሪክ እና በለገጣፎ ተከታታይ ሽንፈት ማስተናገዱ በመሪነት የሚቀጥልበትን እድል አሳጥቶታል ። በዘንድሮው የምድብ ሀ ውድድር ከፍተኛ ፉክክር ከመታየቱም በላይ የሊጉ መሪዎች በየሳምንቱ የሚቀያየርበት ሁኗል።ክለቡን ጥሩ መሻሻል እንዳሳይ ያደረጉት አሰልጣኝ ያሬድ ቶሌራ ባለፈው ሳምንት ያጡትን ነጥብ ለማግኘት እና ከመሪዎቹ ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ቡድናቸውን እየመሩ ወደ ሜዳ ይገባሉ ።በጉዳት ምክንያት በርካታ ተጫዋቾችን ያጣው ደሴ ለነገው ጨዋታ የመድረሳቸው ነገር አጠራጣሪ መሆኑ ለቡድኑ ትልቅ ክፍተት ነው። ተጋባዡ ፌደራል ፖሊስ ባንፃሩ እስካሁን ካደረጋቸው 7 ጨዋታዎች በሶስቱ አሸንፎ በ 1 አቻ እና ሶስት ጊዜ ተሸንፏል ።በአንፃሩ ደሴ 4 አሸንፎ 2 ተሸንፏል ።የጎል ብዛት ስንመለከት ደሴ 9 አስቆጥሮ 4 የተቆጠረበት ሲሆን ፌደራል ፖሊስ 6አስቆጥሮ 8 ተቆጥሮበታል ። ደሴ 13 ነጥብ እና ፌደራል ፖሊስ 10 ነጥብ ይዘው በደረጃ ሰንጠረዡ 4ኛ እና 5ኛ ደረጃ የሚገኙ ሲሆን ከመሪው መከላከያ ያላቸውን ነጥብ ለማጥበብ ይፋለማሉ ። በደሴ በኩል ቶስላች፣አንዋር ፣አብዱ እና አክዌር ለነገው ጨዋታ መሰለፋቸው አጠራጣሪ ነው።

ያለፉትን 3 ጨዋታዎች(ከቅርብ ወደ ሩቅ)
👉ደሴ –ተሸነፈ-ተሸነፈ-አሸነፈ
👉ፌደራል ፖሊስ-አቻ-ተሸነፈ-አሸነፈ
የእርስ በርስ ግንኙነቶች
-እስካሁን በሊጉ አምስት ጊዜ ተገናኝተው ደሴ አራት ጊዜ ፌደራል ፖሊስ ደግሞ አንድ ጊዜ በተመሳሳይ 1-0 አሸንፈዋል ።
-በድምሩ 5 ጎሎች ተቆጥረዋል ።
ግምታዊ አሰላለፍ
ደሴ ከተማ(4-3-3)
ሰለሞን-ሳሙኤል-በረከት-አስናቀ
ኤርምያስ -ዮሴፍ -በድሉ
ልዑልሰገድ -አቡበከር -ብርሃኑ

ቅኝቶቹን የመታደግ ጥሪ

ለቅኝቶቹ ደጋፊዎች በሙሉ

👉የደሴ ከነማ እግር ኳስ ክለብ የበጀት እጥረት አጋጥሞታል ይህን ለመቅረፍ የክለብ ቦርድ የራሱን ስራ እየሰራ ሲገኝ በደጋፊዎቹ ማህበር ደሞ በመጭው ቅዳሜ ገቢ ማሰባሰቢያ ስራ ይሰራል!!!

👉በመጭው ቅዳሜ ሙሉቀን በደሴ ከተማ ሰፈሮች በመዟዟር በደጋፊዎቹ ማህበር በተመረጡ ሰዎች ህጋዊ ደረሰኝ ይዘን በየ ቤታችሁ ልንመጣ ዝግጅታችንን ጨርሰናል!!!!

👉በመጭው ቅዳሜ በየ ቤታችሁ እንመጣለን ደሴ ከነማን መታደግ እፈልጋለሁ የምትል በሙሉ ከወዲሁ ተዘጋጅ ለምን እቤትህ ድረስ መጥተን ክለብን እንድትታደግ ስንል እናሳውቃለን!!!

👉የደሴ ከተማ ህዝብ ደሞ አያሳፍረንም ብየ ተስፉ አረጋለሁ ደሴ ከነማ በአፉጣኝ ይህ የበጀት ችግር መቀረፍ አለበት ስለዚህ ይህን ስራ እንሰራለን!!!!

👉በታሪክ አጋጣሚ ሁኖ ደሴ ከነማን የመታደግ ሀላፊነት ደጋፊዎች ላይ ሁኗል ስለዚህ ደጋፊዎች ተዘጋጁ ቅዳሜ በያላችሁበት እንመጣለን!!!!

👉ደሴ ከነማ የናንተ የኔ የሁላችንም ነው ደሴ ከነማን ለመታደግ ሁላችንም በአንድነት እንነሳ ቅዳሜ እንዳይረሳ!!!

@dessiecityfootballclub

የከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ 7ኛ ሳምንት ውጤቶች

ሀሙስ ጥር 20, ቀን 2013

ደሴ ከተማ 1-2 ለገጣፎ ለገዳዲ
ወልዲያ ከተማ 0-1 ኢትዮ ኤሌክትሪክ

አርብ ጥር 21, ቀን 2013

ወሎ ኮምቦልቻ 0-0 ሰ/ሸ/ደ/ብርሃን
መከላከያ 0-1 ገላን ከተማ
@dessiecityfootballclub

Design a site like this with WordPress.com
Get started